Wednesday, July 30, 2008

"በርግጥ ኢትዮጵያ ላይ ሴራ አለ?"

ይህን ጥያቄ የማነሳው ያለ ምክንያት አይደለም። ጥቂት በማልለው የሕብረተሰባችን ክፍልና አልፎ አልፎም ቢሆን በተቃዋሚ ፓርቲዎች አካባቢ ሲንጸባረቅ የማየው የውጭ ፖሊሲ አዝማሚያ ስለሚያሳስበኝ ነው።

ክርክሬን አጭርና ደፋር በሆነ ዓረፍተ ነገር ልክፈትና “ታላላቅ መንግሥታት የኢትዮጵያን መጠናከርና አንድነት አይፈልጉም” የሚለው አመለካከት ከዘመናችን የፖለቲካ ጭብጥ ጋር የማይገናዘብ በማስረጃ ያልተደገፈ አጉል ስጋት ነው እላለሁ።

ከጭብጡ ጋር የማይገናዘብ ያልኩት ያለንበት ዘመን የኮሎኒያሊዝም መስፋፋትና “አፍሪካን የመቀራመት” ዘመቻ ያከተመበት መሆኑን ለማመልከት ነው። በዚያ ዘመን ኢትዮጵያን ለማዳከምና ግዛቷን ከዚህም ከዚያም ለመቦጨቅ የተጉ መንግሥታት በርካታ ነበሩ። ኢጣልያ፤ እንግሊዝ፤ ፈረንሳይ፤ ቱርክና ግብጽ ማለቂያ በሌለው ጦርነት ውስጥ ጠምደውን ለልማት የምናውለውን ውድ ጊዜና ሀብት ሰርቀውብናል። በሁለተኛ ደረጃ የሚታይ ይሁን እንጅ ግብጽና ሱዳን ዓባይ ወንዝን በተመለከተ ብዙ ይፈታተኑናል። ባካባቢው ከፍተኛ የክርስትና ሀይማኖት ተከታይ የሚገኝባት አገር በመሆኗም አንዳንድ የስልምና ሀይማኖት ተከታይ አገሮች ኢትዮጵያን በፍቅር አያይዋትም። የኋለኞቹ በየራሳቸው ችግር የተጠመዱና ከኃያላን ጋር የማይመደቡ በመሆናቸው ለጊዜው አላተኩርባቸውም።

ዘመኑ የተለዬ ነው፤
አሁን የምንገኘው ፈጽሞ ልዩ በሆነ የዓለም ፖለቲካ ድባብ ስር ስለሆነ የፈለግነውን ያህል ብንጠራጠር፤ ባለፈው በደላችን ላይ ብናላዝንና ብናቄም ላዲሱ ዓለም የኑሮ ፈተናችን የሚጠቅመን ነገር የለም። የዚህ ትውልድ አደራ በመቃ ብዕር የተጻፈና በብራና ላይ የተከተበ ሳይሆን በኮምፒውተር ግራፊክ የተቀረፀ የ21ኛው ክፍለዘመን አደራ ነው።

እራስ የሚያዞር ጥድፊያና በጀርባ የሚያርድ ተወዳዳሪ በበዛባት ዓለም የሀገራችንን ድርሻ ለመሻማትም ሆነ የክብር ቦታዋን ለማግኘት የምናደርገው ትጋት ፋታ መስጠት የለበትም። መመራመር ያለብን ያዲሱ ዓለም የፖለቲካና የኤኮኖሚ ድባብ ምን ይመስላል? በዚህ ድባብ ውስጥ ሁነኛ ተጫዋች ሆነን ለመገኘት በማሕበረሰብ ደርጃ ባቻ ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ ምን ዝግጅት ማድረግ አለብን? በመጀመሪያና በሁለተኛ ደረጃ ከማን ጋር መሻረክ ይኖርብናል? የፓለቲካና የኤኮኖሚ ፖሊሲዎቻችን ወዳጅ፤ ካፒታልና የቴክኖሎጅ ፍሰት እንዲስቡ ምን ምቹ ሁኔታ መፍጠር አለብን እያልን ነው። ለሁለተኛ ጊዜ “በረሳነው ዓለም እንድንረሳ” መፍቀድ የራስን ሕይወት በራስ የማጥፋት ያህል ሀጢአት ይመስለኛል።

በመነሻነት ይህን ያህል ካልኩ በኋላ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የውጭ መንግሥታትን ድጋፍ ለማግኘት፤ በተለይም ደግሞ ወሳኝ ሚና የሚጫወተውን ያሜሪካን መንግሥት ድጋፍና አመኔታ ለማግኘት ያደረጉት ጥረት አመርቂ ነበር ወይ? የሚለውን ልመልከት። መልዕክቴን በቅጡ ለማስተላለፍ ይረዳኝ ዘንድ ጥረታቸው “በቂ አልነበረም” በሚል ድምዳሜ እጀምራለሁ።

የተቃዋሚ ወገኖችና ያሜሪካ አስተዳደር መቃቃር፤
ቁጥሩ ትንሽ የማይባል የዳያስፖራ ነዋሪ፤ እንዲሁም ብዙ የፓርቲ፤ የሀይማኖትና የማሕበራዊ ድርጅት መሪዎች “ታላላቅ መንግሥታት ኢትዮጵያን በማፈራረስ ወይንም በማዳከም ሴራ ውስጥ አሉበት” የሚል አስተሳሰብ ያንጸባርቃሉ። የዚህ ሀሳብ አራማጆች በዋቢነት የሚጠቅሱት ሶማሊያ በ1974 ኢትዮጵያን ስትወር አሜሪካ የተከፈለበትን መሣሪያ አላስረክብም ማለቷን፤ እንዲሁም ወያኔ ሀርነት ትግራይ የሚባል ገንጣይ ቡድን በ1991 አገሪቷን እንዲቆጣጠር መፍቅዳቸውን ነው። ወደኋላ ከተመለስን ሌሎችም ይኖራሉ።

ይሁን እንጅ አሜሪካ ለምን እነዚህን አቋሞች እንደወሰደች፤ ይህ ደግሞ ከራሷ ብሔራዊ ጥቅም አንጻር ለምን ትክክል ነው ብላ እንዳሰበችና ፖሊሲዋ ኢትዮጵያንም ሌሎች አገሮችንም በሚመለከት ወጥነት እንዳለው መረዳት አለብን።

የ1974ቱ አብዮት የኮሚኒዝም ጽንስና የብሔርተኝነት ዝንባሌ ይነበብበት ስለነበር አሜሪካኖቹን ቢያቁነጠንጣቸው አያስገርምም ነበር። ከዚህም ሌላ ሶቪየት ዩኒየን የሶማሊያ ቆይታዋን በማቋረጥ ፊቷን ወደ ኢትዮጵያ ለማዞር እንደተዘጋጀች አሜሪካ ታውቅ ነበርና መሣሪያ መላኩን አቆመች። በዚህ ሁኔታ ለኢትዮጵያ የቀረው አማራጭ ጭልጥ ብሎ ከሶቪዬት ጉያ መግባት ሆነ።

ስለብሔርተኝነት ካነሳን አሜሪካም ሆነች ሌሎቹ ኃያላን መንግሥታት ብሔርተኝነት፤ በተለይ ደግሞ አክራሪ ዓይነቱ ብሔርተኝነት ለምን እንደሚገዳቸው መረዳት ያስፈልጋል። ብሔርተኝነት በባህርይው ገለልተኛና አትንኩኝ ባይ መሆኑ፤ አክራሪ ብሔርተኝነት በዓለም ታሪክ ውስጥ ብዙ ጥፋት ማስከተሉ፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ አክራሪ ብሔርተኛ መንግሥት ባለበት አካባቢ የራሳቸውን ጥቅም ለማስከበር በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ እንቅፋት ስለሚሆንባቸው ፈጽሞ አይፈቅዱትም።

ወደሁለተኛው የቅሬታ መንስዔ ልሸጋገር። ብዙ ሰዎች እንደሚያስቡት አሜሪካ ሕወሀት ሙሉ ሥልጣን እንዲጨብጥ አትፈልግም ነበር። “ሕውሀት በአንድ አነስተኛ ብሔረተስብ የተገነባ ፓርቲ ስለሆነ ሰፊ የሕዝብ መሠረት አይኖረውም፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሕውሀትን የሚመለከተው እንደ ተገንጣይ/አስገንጣይ ሃይል ነውና አመኔታውን አይለግሰውም፤ ራሱ ሕውሀት ጥርሱን ነቅሎ ያደገው በአልባኒያ ኮሚኒስት ፓርቲ ሞግዚትነት ስለሆነ መልካም አስተዳደር በኢትዮጵያ ውስጥ ለማምጣቱ ምን ማረጋገጫ አለን?” የሚሉ ተጨባጭ ስጋቶችን ታስተናግድ ነበር።

የለንደኑ ድርድር፤
ከነዚህ ስጋቶች በመነሳት ነበር አሜሪካ ሕውሀትንና በመፈራረስ ላይ የነበረውን የሁለቱ ተስፋዬዎች መንግሥት (ጀኔራል ተስፋዬ ገብረኪዳንና አቶ ተስፋዬ ዲንቃ) ጥምር የሺግግር አስተዳደር እንዲያቋቁሙ ጥረት ያደረገችው። ሕውሀትና የነተስፋዬ መንግሥት ወደ ድርድር ጠረጴዛ ይዘውት የቀረቡት አቋም የተለያየ ቢሆንም ለማቀራረብ የማይቻል አልነበረም። በብዙ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ተደርሶ በሽግግር መንግሥቱ ውስጥ የጦር ሚኒስቴርን ማን ይቆጣጠርና በሕይዎት ማጥፋት የሚጠየቁ የደርግ ባለሥልጣናት ሁኔታ በምን መልክ ይታይ የሚሉት ጥያቄዎች ድርድርሩን እንዳቆረፈዱት ይነገራል። ይህ በመካሄድ ላይ እያለ በመላ አገሪቱ በተለይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሊፈነዳ የተቃረበ የፀጥታ ሁኔታ ተፈጠረ። አሜሪካኖቹ ለዚህ አሳሳቢ ሁኔታ ቅድሚያ ሰጡና ፀጥታ ለማስከበር የተሻለ ድርጅት የነበረው ሕውሀት ከተማዋን/ሀገሪቷን እንዲቆጣጠር ተስማሙ። “ጦሩ የተፈታውና የሕዝብ ድጋፍ ከድቶት የነበረው የነተስፋዬ መንግሥት በለንደኑ ውይይት ላይ በብልህነት ተደራድሮ ቢሆን ኖሮ ያገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ልዩ መልክ ሳይኖረው ይቀር ነበር?” እያልኩ አንዳንዴ ራሴን አካለሁ።

ታዲያ አሜሪካኖች ለሕውሀት የሰጡት ድጋፍ ገደብ ነበረው። በኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲ ለማምጣት ግዴታ አስገብተውና ይህን ቃል የማያከብር ቢሆን የኤኮኖሚና የዲፕሎማሲ ድጋፍ እንደሚነፍጉት አስጠንቅቀው ነው። የኸርማን ኮኸን “ኖ ዴሞክራሲ ኖ ኤይድ” ከዚህ መነጨ።
እዚህ ላይ “ሕውሀት ላሜሪካኖቹ የገባውን ቃል ሲያፈርስ፤ ጸረ ዴሞክራሲና ጠባብ ፖሊሲዎቹን ሲያራምድ ለምን ካሮታቸውን አልነጠቁትም?” የሚል ጥያቄ ቢነሳ አግባብነት አለው። ለዚህ ጥያቄ መልስ ማግኘት በዲፕሎማሲው መስክ የምናየውን ግድፈት በማጥራት በኩል ይረዳል ብዬ ስለማምን አንዳንድ ነገሮችን አነሳለሁ። ቢያስደስትም ቢያስከፋም።

አንደኛ። አሜሪካ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ካላት የተንሰራፋ ጥቅም፤ ኃላፊነት፤ አቅምና ትዕግሥት አንጻር ለአፍሪካ የምትሰጠው ጊዜ እጅግ አነስተኛ ነው። ስለ አፍሪካም ሆነ ስለያገሮቻችን አበጥ ያለ አመለካከት ያለን ሁሉ ያን አመለካከታችንን ጥቂት ማስተንፈስ አለብን። ኤኮኖሚያዊና ስትራቴጅያዊ ጥቅማቸው አናሳ በሆነባቸው አገሮች የዴስክ ኃላፊ አድርገው የሚመድቧቸው ግልገል ዲፕሎማቶች መሆናቸውን ስናይ በዓለም ፖለቲካ ውስጥ ያለን ቦታ የቱን ያህል የኮሰሰ እንደሆነ እንገነዘባለን።

ሁለተኛ። አሜሪካም ሆነች አውሮፓውያን ትኩረታቸውን የሚስብ አማራጭ ኃይል እስካላገኙ ድረስ ካለው መንግሥት ጋር መዳረቅን ይመርጣሉ። ለምን ብለው ጣጣ ውስጥ ይግቡ? “ተቃዋሚው የተበታተነና አብሮ ለመሥራት የማያመች ነው” እያሉ በመደጋገም ሲናገሩ የምንሰማው ለዚህ ነው። ኃያላን መንግሥታት በየትም አገር ቢሆን ጠንካራ አማራጭ ፓርቲ እንዲኖር መፈለጋቸው እርግጥ ነው። “ትራምፕ ካርድ” ይሉታል እነሱ። ዛሬ አንዱን ነገ ሌላውን ጠጋ በማድረግ ባገሪቱ ላይ ያላቸውን ፖሊሲና ፕሮግራም ያለ ብዙ ውዝግብ ለማራመድ የሚያመቻቸው አማራጭ ሲኖራቸው ነውና። አለያ የ “ስታተስ ኰ ፖለቲካ” መከተላቸውን ይቀጥላሉ።

ሦስተኛ። የዲፕሎማቲክ ፖሊሲ የሚቀረጸው በርካታ ነባራዊ ሁኔታዎች ተገናዝበው ነው። ሀቅ፤ የሞራል እሴቶችና የሕገመንግሥት አንቀጾች ብዙ ሚዛን ላይደፉ ይችላሉ። አሜሪካ በሕገመንግሥቷ ዴሞክራሲን ለማስፋፋትና ለመብት የሚታገሉ ሕዝቦችን ለመርዳት የገባችውን ክቡር ቃል ኪዳን ችላ እያለች አንዳንዴ ከአምባገነኖች ጋር ስትወግን የምናየው አምባገነኖች ስለሚጥሟት ሳይሆን ሁነኛ አማራጭ ስለምታጣ ነው።

ወደለንደኑ ጉባኤ ልመለስና ሌላ አሜሪካኖቹን ያነሆለለ አንድ ግንዛቤ ነበር። “የሕውሀት ኃይል የተገነባው ጠባብ የብሔረሰብ መሠረት ላይ ስለሆነ የሌሎች ብሔረሰቦችን ድጋፍና አመኔታ ለማግኘትም ሆነ ሁነኛ የፖለቲካ ኃይል ሆኖ ለመቆየት በዴሞክራሲ ፋና-ወጊነት የታሪክ ቦታ መቅረጽ ይፈልጋል። ከረጅም ጊዜ ጥቅሙ አንጻር ሲታይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ባለውለታ ማድረግ “ደ!” የሚያሰኝ ጥያቄ ነው” የሚል ሎጅክ-ቀመስ ነገር ግን ገራገርነት የሚነበብበት አቋም ወሰዱ። ኸርማን ኮኸን ስቴት ዲፓርትመንትን ከለቀቁ በኋላ በጻፉት መጽሀፍ ይህ ግንዛቤ ግድፈት እንደነበረውና ሕውሀት ቃሉን ያልጠበቀ አምባገነን መንግሥት መሆኑን በምሬት ገልጸዋል።

በላይኛው የጽሁፌ ክፍል አሜሪካኖቹ ለወሰዱት አቋም ምንና ምን ታሳቢ አድርገው እንደነበር የማውቀውንና የሚመሰለኝን ያህል ላስጨብጥ ሞክሬያለሁ። ዛሬ ላይ ሆኘ ሳየው በአጭሩ ጊዜ አሜሪካ ያገሯን ጥቅም ችላ ብላ ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ስርጸት መቆም ይገባታል እያልን ባደባባይ መዝለፋችን ትክክል አልነበረም፤ ያተረፍነው ነገር የለምና። በሌላ በኩል ደግሞ አሜሪካኖቹ የሕውሀት ፕሮፓጋንዳ ሰለባ ሆነው ተቃዋሚው ወገን አክራሪ ብሔርተኛ ነው፤ የደርግ ርዝራዥ ነው፤ የአማራ ስብስብ ነው በሚል አሳፋሪ የቀለም ቅብ ውስጥ መሳተፋቸው የጥፋትም ጥፋት ነበር።


ላጠቃል፤
ታላላቅ መንግሥታት በኢትዮጵያ መዳከምም ሆነ መበታተን የሚጠቀሙት አንዳችም ነገር ስለሌለ ይህን ዘመን ያፈጀ አስተሳሰብ መላቀቅ አለብን። በኤኮኖሚና በሚሊተሪ የዳበረች፤ ላካባቢው መረጋጋት አስተማማኝ ኃይልና አጋር የምትሆን ኢትዮጵያን ይመርጣሉ ብሎ ማሰብ ይበልጡን ሚዛን ይደፋል። ከዚህም ሌላ 80 ሚሊዮን ሕዝብ ሠላምና መረጋጋትን አግኝቶ የነፍስ ወከፍ ገቢውን ቢያሳድግ ታላቅ ገበያና ታላቅ ወገን ተፈጠረ ማለት ነውና አሜሪካም ሆነች ሌሎቹ አይከፉም። በአንጻሩ ደግሞ ከኢትዮጵያ መራብ ያሚተርፋቸው ነጻ የስንዴ ርዳታ ማመላለስ ብቻ ነው። ከኢትዮጵያ የእርስ-በርስ ግጭት የሚያገኙት በሚዘገንን የነፍስ አድን ዘመቻ ውስጥ መዘፈቅ ብቻ ነው።

ራዕያችን በምንመኘው ደረጃ ድጋፍ ሳያስገኝ ቀርቶ ከሆነ ጥፋቱ የኛ እንጅ የነርሱ አይመስለኝም። ራዕይ ስሜትን በሚነካ መልክ ተቀርጾ፤ በማለፊያ የዲፕሎማሲ ጥበብ ተጠቅልሎ ከተወዳዳሪ ራዕዮች በልጦ መገኘት አለበት። የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት ጥረታችን “የኛን ሀሳብ ተቀበሉን፤ የኛን ጭኸት ስሙን” ከሚለው ረድፍ ወጥቶ ለምንና በምን ምክንያት እኛ የተሻልን አማራጭ እንደሆንን፤ እንዴትስ የፖለቲካ፤ የኤኮኖሚ፤ የዕምነት፤ የስትራቴጅና የደህንነት መሥመራችን ከነርሱ መስመር ጋር እንደሚጣጣም በማሳመን ላይ ያተኮረ ሊሆን ይገባል።

በሌላ በኩል ደግሞ ራዕይና ፖሊሲ ጥቅል ስለሆኑ “ግሩም!” ከመባል ያለፈ አድናቆትን አያስገኙም። ቁምነገሩ ያለው ከዝርዝሩና ፈረንጆቹ “ብርንዶውን አሳየኝ” ከሚሉት ላይ ነውና ያፈጻጸም ፕላንና ይህን በተግባር ለመተርጎም የሚችል ሰፊ የድጋፍ መሠረት ያለው ድርጅት እንዳለን ማሳመን ግዴታችን ይሆናል።

ድጋፍ ማግኘትና አጋር ማብዛት ብዙ ሥራ፤ ብዙ ስልት፤ ብዙ አንደበተ-ርቱዕ ዲፕሎማቶች፤ ብዙ ትዕግሥትና ብዙ ሺር-ጉድ ይጠይቃል። ኃያላን መንግሥታት ሳይቀሩ አንዱ በሌላው ላይ ካልተደገፈ ብቻቸውን መቆም አይችሉምና የወዳጅ ክበባችንን በውል እናስፋ። ይህ “በራስ መተማመን” የምንለውን ክቡር መርህ የሚያኮስስ ሳይሆን ውጤታማነቱን የሚያፋጥን መሆኑንም አንሳት።

ወዘተርፈ…(የኦባማ ጉዳይ)
ሰሞኑን የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን ያገባደዱት ያሜሪካ ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዴቪድ ክሬመር ኢትዮጵያን በተመለከተ ያሜሪካ የውጭ ፖሊሲ መሠረታዊ ለውጥ እንደማይኖረው አስገንዝበዋል። ከኦባማ መመረጥ ጋር ብዙ ተስፋ ለምናደርግ ጥሩ ማስጠንቀቂያ ይመስለኛል።

ዴቪድ ክሬመር ድረስ ሳልሄድ በጥልቅ ትንታኔውና በወዛም አቀራረቡ የሚታወቀው የኛው “ኢትዮ ፐንዲት” www.http://ethiopundit.blogspot.com/ ጁን 29 ባስነበበው ጽሑፍ ኢትዮጵያን በተመለከተ ያሜሪካ ፖሊሲ ይለወጣል ብሎ ማሰብ አደጋ እንዳለው አስጠንቅቋል። “ዴሞክራቶቹ ቢል ክሊንተን፤ ማደሊን ኦልብራይት እና ሱዛን ራይስ ከመለስ ዜናዊ ጋር የነበራቸው መሞዳሞድ በሪፐብሊካኑም አስተዳደር ቀጥሎ ቡሺ፤ ኮንደሊዛ ራይስ፤ ቪኪ ሄንደርሰንና ጀንዳይ ፍሬዘርም የመለስ አሳዳሪ ሆነው ሰንብተዋል” ይላል። በመቀጠልም “ጆን ማኬን ከዚህ የተለየ ፖሊሲ ይከተላል ብሎ ማሰብና የመለስ ደጋፊና አሁን የባራክ ኦባማ የውጭ ግንኙነት አማካሪ ሆና የምታገለግለው ሱዛን ራይስ ኦባማ በዜናዊ ላይ ፊቱን እንዲያዞር ትማጸናለች ብሎ መጠበቅ አስቸጋሪ ነው” በማለት ይደመድማል።

አዘለም አንጠለጠለም መልዕክቱ ፓርቲዎች ቢለዋወጡ እንኳ ያሜሪካ የውጭ ፖሊሲ ይህን ያህል መሥመሩን አይስትም ለማለት ነው። ገና ብዙ ሥራ ይጠብቀናል ለማለትም ነው።

kuchiye@gmail.com

2 comments:

T. Brehan said...

Kuchiye,

While the issue you raise is thought-provoking, and indeed our struggle against minority tyranny won’t go very far if it is limited to armchair philosophizing, the contributions of intellectual giants like Prof. Al Mariam cannot at all be under-estimated.

What we need is more and more people like Professor Al tackling the various theoretical as well as practical issues facing Ethiopians in the struggle to get rid of Woyane. Actually, the problem right now is we don’t have enough Al Mariams out there.

Aside from the fact that Professor Al Mariam is an active participant in the struggle for democracy in Ethiopia including his prominet role in ESAT broadcasting, in presenting papers at various forums, in his several appearances at demonstrations, in his invaluable service during the time our leader Birtukan Mideksa was in the United States, ad infinitum, Professor Al Mariam serves a major contribution: More than distributing guns and weapons for soldiers, his effort educates the mind of the soldier, the fighter, the demonstrator, those who approach foreign governments to convince them that they are wrong in supporting tyranny in Ethiopia.

Professor Al Mariam arms all these pepole with the intellectual footing they need, the strategies they should follow, the facts that support their struggle, the vision of what a future Ethiopia should and would be, and the machinations, tricks, and duplicities of the tyrant, Meles.

What we need more is not just people who carry guns, but active soldiers with an commitment, intellect, enlightenment, devotion, and determinaiton to carry the day. It is pepole of of those who carry the guns that will win the war in any confrontation.

Don’t forget, the idea is not just to win wars, but more rather to win minds. We should be able to convince supporters of Woyane, that their way is the wrong way, thier struggle is destructive, that their thoeries and intellectual positions do not hold water or stand the test of logical analysis, their leaders are tryants leading them to bloodshed and destruction, etc.

What Woyane is currently trying to do is win legitimacy among Ethiopians. Despite staying in power for 20 years, no Woyane official can safely and confidently address an Ethiopian gathering since the Woyanes are intellectually bankrupt and they are ruling by force of arms and not by convincing the populace.

What Professor Al Mariam and his likes are doing is keeping the upper hand in the struggle for the souls and minds of Ethiopians, and they have so far succeeded. Imagine to what low level Woyane has to go during the the 2010 election to win peoples’ votes: and remember Professor Al Mariam’s article where he declared “The Emperor is naked!!”

The more we can convince Tigrean and other supporters of Woyane that their way is the wrong way, and that Ethiopianess cannot be stopped but shall triumph, the less human resource the Woyanes will get to implement their evil ways, and eventually it is possible Woyane will give up since it becomes so clear that it is an intellectually bankrupt organization.

It is people like Professor Al Mariam who are intellectual giants who can do jobs like that effectively. Do not underestimate the power of education, knowledge, information, logical analysis, convincing arguments. It can disarm giant armies and lead to a less-violent solution.

I do appreciate your thought-provoking article, but in terms of being critical towards Professor Al Mariam, Professor Messay, Genet Mersha, etc., you article and opinion is way off-mark.

T. Brehan said...

Kuchiye,

While the issue you raise is thought-provoking, and indeed our struggle against minority tyranny won’t go very far if it is limited to armchair philosophizing, the contributions of intellectual giants like Prof. Al Mariam cannot at all be under-estimated.

What we need is more and more people like Professor Al tackling the various theoretical as well as practical issues facing Ethiopians in the struggle to get rid of Woyane. Actually, the problem right now is we don’t have enough Al Mariams out there.

Aside from the fact that Professor Al Mariam is an active participant in the struggle for democracy in Ethiopia including his prominet role in ESAT broadcasting, in presenting papers at various forums, in his several appearances at demonstrations, in his invaluable service during the time our leader Birtukan Mideksa was in the United States, ad infinitum, Professor Al Mariam serves a major contribution: More than distributing guns and weapons for soldiers, his effort educates the mind of the soldier, the fighter, the demonstrator, those who approach foreign governments to convince them that they are wrong in supporting tyranny in Ethiopia.

Professor Al Mariam arms all these pepole with the intellectual footing they need, the strategies they should follow, the facts that support their struggle, the vision of what a future Ethiopia should and would be, and the machinations, tricks, and duplicities of the tyrant, Meles.

What we need more is not just people who carry guns, but active soldiers with an commitment, intellect, enlightenment, devotion, and determinaiton to carry the day. It is pepole of of those who carry the guns that will win the war in any confrontation.

Don’t forget, the idea is not just to win wars, but more rather to win minds. We should be able to convince supporters of Woyane, that their way is the wrong way, thier struggle is destructive, that their thoeries and intellectual positions do not hold water or stand the test of logical analysis, their leaders are tryants leading them to bloodshed and destruction, etc.

What Woyane is currently trying to do is win legitimacy among Ethiopians. Despite staying in power for 20 years, no Woyane official can safely and confidently address an Ethiopian gathering since the Woyanes are intellectually bankrupt and they are ruling by force of arms and not by convincing the populace.

What Professor Al Mariam and his likes are doing is keeping the upper hand in the struggle for the souls and minds of Ethiopians, and they have so far succeeded. Imagine to what low level Woyane has to go during the the 2010 election to win peoples’ votes: and remember Professor Al Mariam’s article where he declared “The Emperor is naked!!”

The more we can convince Tigrean and other supporters of Woyane that their way is the wrong way, and that Ethiopianess cannot be stopped but shall triumph, the less human resource the Woyanes will get to implement their evil ways, and eventually it is possible Woyane will give up since it becomes so clear that it is an intellectually bankrupt organization.

It is people like Professor Al Mariam who are intellectual giants who can do jobs like that effectively. Do not underestimate the power of education, knowledge, information, logical analysis, convincing arguments. It can disarm giant armies and lead to a less-violent solution.

I do appreciate your thought-provoking article, but in terms of being critical towards Professor Al Mariam, Professor Messay, Genet Mersha, etc., you article and opinion is way off-mark.