Thursday, November 15, 2007

የቅንጅት መሪዎች የሚመለሱት በፍቅር ወደተሞላው የወገናቸው እቅፍ ውስጥ ነው!

የ 97 ምርጫ ይዞት ከመጣው ተስፋም ሆነ ካስከተለው ፀፀት ያልተማረ የለም ቢባል ስህተት አይሆንም። “ፕሮግራሜ በመላው ኢትዮጵያ ተቀባይነት አለው፤ ለሕዝብና ከሕዝብ ጋር የቆምኩ ነኝና ምርጫ ቢከናወን በአሸናፊነት እወጣለሁ” ብሎ ያስብ ከነበረው ከኢሕአዴግ የበለጠ ከዕንቅልፍ የሚገፈትር ማንቂያ አግኝቷል። ለዚህም ነበር በምርጫው የደረሰበትን ኪሳራ ለመገምገም ካድሬዎቹን፤ የደህንነት ሠራተኞቹንና ሌሎች በመላ ሀገሪቱ የበተናቸውን ባለዳረጎቶች በምርጫው ማግሥት ሰብስቦ ማፋጠጥ የጀመረው። በዚያው ሰሞን በየወረዳውና በየነጥብ ጣቢያው ሳይቀር ሕዝቡን ሰብስቦ “ምን በድለናችሁ ነው እንዲህ የገፋችሁን?” እያለ ተማጸነ። ገበሬውና ነጋዴው፤ ተማሪውና አስተማሪው፤ ከተሜውና ገጠሬው ብሶታቸውን ባንድ ድምጽ አሰሙ…..

“ሕዝብን የመለያየት ፖለቲካችሁን አቁሙ!”
“ያንድ ወገንን የበላይነት በሌሎች ላይ ለመጫን የምትፈጽሙት ዓይን ያወጣ ነውር ያብቃ!”
“ካድሬዎቻችሁ ወታደሮቻችሁና ሹሞቻችሁ የሚያደርሱት ወከባ ኢትዮጵያዊነታችንን አጠራጥሮናል!”
“መሬትን የፖለቲካ መሣሪያ አታድርጉ!”
“ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻችን ይከበሩ”
“ነጻ ፍርድ ቤቶች፤ ነጻ ምርጫ ቦርድ፤ ነጻ ሠራዊት፤ ነጻ ፕሬስ… !” ወዘተ

ገዥው ፓርቲ እነዚህን የሕዝብ ቅሬታዎች አላዳመጠም ማለትና ግዙፍ ስህተቶች መፈጸሙ አልረበሸውም ማለት ጭራሹን ማሰቢያ አዕምሮ አልፈጠረበትም ማለት ይሆናልና እዚያ ድረስ መሄድ ስህተት ነው። ጥያቄው መሆን ያለበት በስህተቶቹ ላይ የርምት ርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ሃቀኛነት፤ ወኔና የፖለቲካ ብስለት አለው የለውም ከሚለው ላይ ነው። የታሪክን ማህደር ስንመረምር በመሣሪያ ኃይል ሥልጣን ከያዙ በኋላ ከስህተታቸው ተምረው ለዴሞክራሲ ጥርጊያ መንገድ የከፈቱ ጥቂቶች ናቸው። እነዚህ ወገኖች ራሳቸውን የማታለል አባዜና “ሁሉም አልጋ ባልጋ ነው” የማለት በሽታ ያጠቃቸዋል። ኢሕአዴግ ለዲሞክራሲ ጥርጊያ ከከፈቱት የታሪክ ክበብ ውስጥ የመመደብ ዕድል እንዲገጥመው የማይመኝ ያለ አይመስለኝም። እስከዚያው ግን መንግሥት ከ 97 ምርጫ ተምሬ በተወካዮች ምክር ቤት፤ በምርጫ ቦርዱና በሌሎች ተቋሞች ውስጥ ማሻሻያ አድርጌአለሁ የሚላቸው ርምጃዎች እጅግ ቢበዛ የይስሙላ አለዚያም ማደናገሪያዎች ናቸው። የሚጠቅሳቸው ማሻሻያ ተብየዎች ቀናነት የሚጎድላቸው፤ በፈንጅ የታጠሩና የዴሞክራሲን እድገት ፈቀቅ እንኳ የማያደርጉ ናቸው።

ቅንጅትና መሪዎቹ የፍትህ እጦት ሰለባ ሆነው ለሁለት ዓመታት በእስር የተንገላቱት የሠላማዊ ትግል መርሆችን ተከትለው ዲሞክራሲን ለማምጣት ስለታገሉ ብቻ ነበር። መላ ቤተሰባቸውና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ከነርሱው ጋር ታስሮ ከነርሱ ጋር ተፈቷል ማለት ይቻላል። ራሱ ኢሕአዴግም ከህሊና እስር ለመውጣት ዕድል አግኝቷል ማለት ይቻላል።

የተከፈለው የሕይወት፤ የመንፈስና የማቴሪያል መስዋዕትነት ዋጋ የሚያገኘው በሀገራችን የሰፈነውን የውጥረትና የጥርጣሬ አየር አስወግደን የሚቀጥለውን የዲሞክራሲ ምዕራፍ በአዲስ ቀለም ለመጻፍ በቀና ልቦና መሥራት ስንጀምር ብቻ ነው። ለዚህ ደግሞ መነሻውም መድረሻውም በጠረጴዛ ዙሪያ የሚደረግ ስልጡን ፖለቲካ ነውና የስጋት፤ የበቀልና የጥላቻ መንፈስን ወርውረን ሁሉም አሸናፊ የሚሆንበትን የፖለቲካ ቀመር ማስላት አለብን። በሠላማዊ ትግል የምናምን ሁሉ ከዚህ ውጭ ፖለቲካ ሊታሰበን አይችልም። የሠላም አየርን ለሚማለድ ሕዝባችንም ሆነ በተደጋጋሚ ሰቆቃ ለተጎሳቆለች ውድ ሃገራችን ከዚህ የከበረ የሚሊኒየም ገጸበረከት ልንሰጣቸው አንችልም።

ምንጊዜም መዘንጋት የሌለብን ቁም ነገር ግን የዜጎችን መብት የሚያረጋግጥ መልካም አስተዳደር ከሌለ ብሔራዊ ደህንነት እንደማይኖር ነው። ለዚህ ደግሞ የመልካም አስተዳደር መሠረቶችን መገንባትና ማጠናከር አማራጭ የለውም። ከተጽእኖ ነጻ የሆኑ ፍርድቤቶች፤ ሕግ አውጭውና ሕግ አስፈጻሚው አንዱ ሌላውን የሚቆጣጠርበት ሥርዓት፤ የብዙሃን ፓርቲዎች መቋቋም፤ ሕገ መንግሥትን ማክበር፤ የንግግርና የመሰብሰብ ነጻነትን ማክበር፤ ዜጎች በሠላም ሠርተው የሚገቡበት፤ ብልጽግናና ደስታን የመሻት ተፈጥሮዋዊ ፍላጎታቸውን የሚያሟሉበት የፖለቲካ አየር መፍጠር ግዴታ ነው።

ቅንጅትና መሪዎቹ ከላይ የተጠቀሱትን ቋሚ እሴቶች ለመገንባት በሚደርግ ብሔራዊ ጥረት ውስጥ ከሁሉም ወገኖች ጋር ለመሥራት ቀና መንፈስ ብቻ ሳይሆን ቁርጠኛነቱም እንዳላቸው አስመስክረዋል። የትናንቱ ጥፋትና ጉስቁልና ከትምህርት ሰጭነቱ ባሻገር ሚዛን የሚደፋ ፋይዳ የለውምና ዞር ብለው ወደኋላ የማየትና የማላዘን ፍላጎት የላቸውም። ይህንንም ዋሺንግተን ዲሲ ሴፕቴምበር 16 ቀን 2007 ባደረጉት ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ አረጋግጠዋል። የሃገራችን አጣዳፊ አጀንዳዎች መላ ጊዜያችንን፤ ጉልበታችንንና ዕውቀታችንን በዛሬው ችግሮቻችንና በነገው ብሩህ ተስፋችን ላይ እንድናተኩር የሚያስገድዱ ናቸው።

በአንጻሩ ደግሞ ኢሕአዴግ አንዳንድ መሰናክሎችን እዚህና እዚያ እየወረወረ፤ እርባና የሌላቸው የሕግና ያስተዳደር ሰበቦችን እየጠቀሰ የብዙ ሚሊዮኖችን ሠላማዊ ፓርቲ እንቅስቃሴ ለመግታት የሚያደርገው አሰልች እንካስላንቲያ ኢሕአዴግንም ሃገርንም እንደማይበጅ ከታሪክ ሊማር ይገባል።

የቅንጅት መሪዎች ዓለም አቀፍ ተልዕኳቸውን አጠናቀው ወደሃገራቸው እየተመለሱ ባሉበት በዚህ ሰሞን መንግሥት ለሰብአዊ መብትና ለዲሞክራሲ ግንባታ ያለው ተአማኒነት በገሃድ ይመዘናል። የቅንጅት መሪዎች የሚመለሱት ወደሞቀውና በፍቅር ወደተሞላው የወገናቸው እቅፍ ውስጥ ነው። የሚያራምዱት የሠላማዊ ትግል፤ የብሔራዊ እርቅና በመቻቻል ላይ የተመሠረተ ሁሉን-አቀፍ የዲሞክራሲና የግንባታ አጀንዳ ነው። የሚቀነስም የሚደመርም ስውር አጀንዳ የላቸውምና ኢሕአዴግ ቡናውን አሽትቶ በቀናው ጎዳና መጓዝን ይምረጥ እንላለን።

የኢትዮጵያ ትንሣኤ አሁን ነው!

kuchiye@gmail.com

Monday, September 03, 2007

"የሚሊኒየም በረከቴ!"

ይድረስ ባገር ፍቅር ለነደድከው
የወገን ትንሣዔን ለተማለድከው፤

“የዴሞክራሲ ፀዳሉን
የመብት ፀጋውን
ያንድነት ምልአቱን
የፍቅር ጽናቱን
ወገኔ ሳይጎናጸፍ
በልማት ጎዳን ሳይከንፍ
ቃል ኪዳኔን አላጥፍም!
የትውልድ አደራዬን
የሰብዕና ሚዛኔን”

ላልከው ለወጣቱ
ለተከበርክ አዛውንቱ
ይድረስህ መልካም ምኞቴ
የምዕተ ዓመት በረከቴ!

ኩችዬ

Monday, January 15, 2007

Why it is strenuous to be an EPRDF fan.
By Kuchiye – January 15, 2007
kuchiye@gmail.com


I consider myself fairly balanced in most aspects of human demeanor. Keeping an open mind, avoiding being judgmental, believing in the power of discourse, self respect, respect for the values of others, sensitivity to real or imagined fears– these, in no particular order, are among attributes I consider important in any decent human being and in contemporary Ethiopian politics. Divisiveness, rhetoric, mediocrity, lack of dignity, name calling, holier-than-thou posturing and win-lose prototypes are among my turn-offs.

Recently, I swung into one of those “self-assessment” moods and tried to seek the rationales that made me a Kinijit supporter
www.ethiomedia.com/access/why_i_support_kinijit.html. Over the new-year weekend, I could not get over the persistent nagging of my conscience to continue with the “self-assessment” exercise. Hence, I began to reflect on why I find myself skeptical about EPRDF and why, indeed, the majority of Ethiopians find it strenuous to bring EPRDF into their fold. Here is what came out of my brain storming exercise:

EPRDF willingly landlocked the country and surrendered the right of 80 million people to access the sea. By admission of its top party brass, EPRDF forced EPLF to abandon the peace negotiation with the Derg government and facilitated Eritrea’s independence.
It surrendered the entire Eritrea only to turn around and fight an outdated trench war that claimed the lives of 70,000 citizens. This, over a piece of land that is of little consequence. In an even more perplexing saga, EPRDF surrendered sovereignty of that same piece of land to Eritrea - the Algiers Accord.


EPRDF exploits the ethnic differences of its people as a weapon of divide-and-rule. It cultivates mafia-type interest groups in regional administrations fully knowing that once these groups are entrenched, they will fight not for the people they are supposed to represent, but for the status-quo and for their circle of friends.

EPRDF dared to take a chance at democracy but lacked the wherewithal to accept the outcome. By so doing, it squandered an amazing legacy that would have gone EPRDF’s way. The killing of peaceful demonstrators, the mass arrests, the ban on independent media, are not exactly the types of incentives that inspire confidence and popular embrace.

EPRDF suffers from a clear case of paranoia. Therein might one find explanation for most of its shortcomings: political philosophy that is founded on ethnicism, propaganda strategy the boarders fear mongering, economic policy that endows the ruling party and its clique but denies the citizen, fear of creating political space to accommodate genuine opposition, habit of holding others accountable for its own ills.

For EPRDF, human and democratic rights are inconvenient truths that have to be recited on world political stages to satisfy the minimum requirement of donors. How else can one explain the absence of press freedom and the totally suffocating political climate Ethiopians are forced to live in? Isn’t this the reason also why Ethiopia is branded as one of the most press unfriendly countries in the world and a leading human rights violator?

Here comes my fairly balanced side. No doubt EPRDF inherited some of the country’s problems, but it was and still is in a historic position to mitigate them. No doubt, also, some progress is made in selected development endeavors, albeit in limited fashion. School enrolment, gross health coverage, road miles etc have improved in absolute terms but as measured by human development Index, which the UN says, is a broader definition of wellbeing, Ethiopia ranks 169th out of 177 countries.

The ultimate optimist in me says there is still time to right the wrong and to build a vitally necessary level of trust between all the parties who have vested interest in Ethiopia. If we dare to spell out what is important for each one of us and what we are fearful of, if we put down our guard and engage in decent discourse, if we show willingness to consider ways and remedies outside of our comfort zones, then we will no doubt be rewarded with a much needed breakthrough. Let’s try the wisdom of queen Sheba, the enormity of Yohannes, the benevolence of Menelik, the progressiveness of Haile Selasssie, the pride of Tona and Jifar, the cunning of Habte Georgis, the daring of Balcha and the humility of all our ancestors. What good is a generation that is not worth a legacy?




,