Monday, September 03, 2007

"የሚሊኒየም በረከቴ!"

ይድረስ ባገር ፍቅር ለነደድከው
የወገን ትንሣዔን ለተማለድከው፤

“የዴሞክራሲ ፀዳሉን
የመብት ፀጋውን
ያንድነት ምልአቱን
የፍቅር ጽናቱን
ወገኔ ሳይጎናጸፍ
በልማት ጎዳን ሳይከንፍ
ቃል ኪዳኔን አላጥፍም!
የትውልድ አደራዬን
የሰብዕና ሚዛኔን”

ላልከው ለወጣቱ
ለተከበርክ አዛውንቱ
ይድረስህ መልካም ምኞቴ
የምዕተ ዓመት በረከቴ!

ኩችዬ