Thursday, October 22, 2009

የአውራዎች አንድነት!
“በዚያን ሰሞን የ “አውራን” አስፈላጊነት ላዋያችሁ ብዬ ብዙ ጥይት ነው ያባከንሁት። ዳግማዊ ዳዊት በተመጠኑ የሥነ-ግጥም ቃላት መልዕክቱን ደህና አድርጎ ስላቀረበው አንብባችሁ ትደሰቱበት ዘንድ ለጥፌዋለሁ።” ኩችዬ
-----------
ጃርት የሚባል አውሬ-ግፍ ቢያበዛበቸው
ንቦቹ ወጡና- ከየመኖሪያቸው
ጥያቄ አቀረቡ- ለየአውራዎቻቸው።
ስብሰባ - ቁጭ አሉ፣
በስፋት - መከሩ።
አውራዎቻቸውን- ፊት ለፊት ቁጭ አርገው
እንዲህ ነገሩዋቸው
እንዲተባበሩ
መሪወቹ ሁሉ
አውራወች በሙሉ - በአንድነት ከሰሩ
ክፉ ጃርት አይመጣም - በዚህ በሰፈሩ።
ቃልም ተገባቡ-ከዚህ ቃል ላይወጡ፣
ለአናቢው ገበሬ-ትዕዛዝንም ሰጡ
አንተ ንብ አናቢ-ከዛሬ ጀምረህ
አሳየን ብለናል- በአንድ ቀፎ አድርገህ።
አናቢው ገበሬ- ልቡ እያመነታ
ትናንት በሚያውቀው- በለመደው ፋንታ
አንድ ቀፎ መርጦ- በጭስ አጠነና
ንቦችን በመለ- ከአውራወቹ ጋራ
በአንድ አስቀመጣቸው
እንደጥያቄያቸው።

ያለ አፈጣጠሩ
ሆኖ ትብብሩ
እያንዳንዱ መሪ-ሰራዊቱን ይዞ
ቀፎው ባዶ ቀረ- ንብ ሁለ ተጉዞ።
ድሮም ሆኖ አያውቅም፣
ትናንት ሆነ ዛሬም
አንድ የንብ አውራ ነው- ከሺህ ሰራዊት ጋር
ውጤትን የሚያሳይ- የሚጋግረው ማር፡፡

ዳግማዊ ዳዊት
ጥቅምት 2002
Ethio_dagmawi@yahoo.com

No comments: